Events | ዝግጅቶች

 

Welcome to our Events page! This is the page where you can find upcoming services, celebrations, fasting periods, various spiritual programs, and community gatherings at St. Teklehaimanot Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Ottawa.

እንኳን ወደ ዝግጅቶች ገፃችን በደህና መጡ! በኦታዋ ቅዱስ ተክለሃይማኖት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያሉትን መጪ አገልግሎቶች፣ ክብረ በዓላት ፣ አጽዋማት ፣ የተያዩ መንፈሳዊ መርሃግብሮች እና  የማህበር ስብሰባዎች የሚያገኙበት ገጽ ነው።

Loading Events

« All Events

Youth Conference 2025 – Eastern Canada Orthodox Churches

August 29 - August 31

We would be honored to invite you to this special spiritual conference (Gubae) organized by the Ottawa St. Teklehaimanot Sebeka Guba. This gathering, scheduled for August 29-31, 2025, at St. Teklehaimanot Ethiopian Orthodox Church, is designed to uplift the spiritual and social well-being of Ethiopian Orthodox youth in Eastern Canada. The conference is organized under the guidance of His Holiness Abune Dimetros.

The theme of the Gubae: “Let Us Keep Our Coming Together”

“And let us consider how we may spur one another on toward love and good deeds, not giving up meeting together, as some are in the habit of doing, but encouraging one another—and all the more as you see the Day approaching.” (Hebrews 10:24-25)

The main objective of the conference is to enhance the spiritual and social life of our youth within the Orthodox Christian faith.

Conference Details:

  • Dates: August 29-31, 2025
  • Location: St. Teklehaimanot Ethiopian Orthodox Church, Ottawa, ON

Schedule:

  • Day 1 (Friday): Prayer and youth sessions at 9:00 AM. “Remember your Creator in the days of your youth…” (Ecclesiastes 12:1) “Train up a child in the way he should go…” (Proverbs 22:6)
  • Day 2 (Saturday): Liturgy in English, teaching sessions, town tour, and separate sessions for adults and kids. “Let the little children come to me…” (Matthew 19:14)
  • Day 3 (Sunday): Annual Fest, liturgy, preaching, lunch, and final blessing by His Holiness Abune Dimetros. “How good and pleasant it is when God’s people live together in unity!” (Psalm 133:1)

በሚመጣው የበጋ ወቅት የኦቶዋ ደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ በአባታችን በብጹ አቡነ ዲሜጥሮስ መመሪያ መሠረት በምስራቅ ካናዳ ሀገረ ስብከት ስር ለሚገኙ ወጣቶች ኦርቶዶክሳውያን ልዩ የአንድነት ጉባኤ  እያዘጋጀ ይገኛል:: በቤተ ክርስቲያናችሁ የሚሳተፉ ወጣት አባላት በጉባኤው ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ጥሪ እናስተላልፋለን::

 

የጉባኤው ጭብጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተመስርቶ መሰብሰባችንን አንተው” የሚል ሲሆን፥ ይህም በዕብራውያን 10፥24-25 ላይ እንደተጻፈው ነው፦ “ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው፥ ነገር ግን እርስ በርሳችን እንመካከር፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።”

 

የዚህ ጉባኤ ዋና ዓላማ በምስራቅ ካናዳ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ሃይማኖታዊና ማህበራዊ ህብረታቸውን ማጠናከር የእናት የአባቶቻቸውን ፈለግ በመከተል በሃይማኖታቸው ጸንተው ሀይማኖታቸውንና ቤተክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁና ለትውልድ እንዲያስተላልፉ ማድረግ ነው::

የጉባኤው ዝርዝር መረጃ፦

  • ቀናት፦ ከዓርብ ነሐሴ 29 እስከ እሑድ ነሐሴ 31 (August 29-31)
    • August 29-31 (የሚጀምረው Augest 29 ጠዋት ሲሆን August 28 ገብቶ ማደር ይቻላል)
    • August 31 የቅዱስ ተክለሃይማኖት አመታዊ የንግሥ በአል ይከበራል::
    • August 31: ሁላችሁም ምዕመናን – ሕፃናት፣ ወጣቶችና ጎልማሶች – እንዲሁም የቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆች በዚህ የተቀደሰ በዓል ላይ እንድትገኙ በአክብሮት እንጋብዛለን።
  • ቦታ፦ ኦታዋ ደብረ ብርሃን ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 915 Merivale Rd, Ottawa, ON K1Z 6A1
  • ዋና ዋና ይዘቶች (አብዛኛው የወጣቶች አገልግሎት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ነው):-
    • ቅዳሴ
    • ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት
    • ዝማሬ
    • የእርስ በእርስ መተዋዋቅና የሀሳብ መለዋወጥና ውይይቶች
    • የጥያቄና መልስ ውድድር
    • የከተማ ውስጥ ጉብኝት

ማሳሰቢያ 1 – በጉባኤው መሳሳፍ የሚፈልጉ ወጣቶች ማሟላት ያለባቸው

  1. ከተላኩበት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል ወይም የምትችል
  2. እድሜያቸው ከ15 ዓመት በላይ
  3. ትራንስፖርት ራስን መቻል
  4. በቤተክርስቲያን ውስጥ ወይም በበጎ ፈቃደኛ ምእመናን ቤተሰብ ጋር ለማደር ፍቃደኛ የሆነ ወይም የሆነች:: በራሳቸው ወጪ ከፍለው በሆቴል ለማረፍ ወይም ለማደር ለሚፈልጉ አስቀድሞ ቢያሳውቁን ለማመቻቸት እንችላለን::
  5. የምግብ ኣለርጅ ካላቸው ቀድሞው ማሳወቅ
  6. የበዓሉን ዝግጅት በተመለከተ የቅርብ ጊዜ መረጃዎችን ለማግኘትና ለመወያየት ይህንን የ WhatsApp ግሩፕ መቀላቀል፡ https://chat.whatsapp.com/EpkjFMoaF6D0iOqp12VsB8

ማሳሰቢያ 2 – ከተሳታፍ አብያተክርስቲያና የሚጠበቅ፦

  1. ለጉባኤው ዕቅድ ዝግጅት ያመቸን ዘንድ ከቤተክርስትያናቸው ለመምጣት ፍላጎት ያላቸው ወይም ፈቃደኛ የሆኑ ወጣቶችን ከላይ በተጠቀሱት ነጥቦች መሠረት እስከ May 30, 2025 ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑትን በመለየት ቁጥራቸውን በጾታቸው ለይቶው እንዲታሳውቁን እንጠይቃለን::
  2. በተጨማሪም በጉባኤው ለመሳተፍ ፈቃደኛ ከሆኑት ወጣቶች ውስጥ አንድ ተወካይ በመመደብ በጉባኤው ዝግጅት ተሳትፎ እንዲያደርጉ መረጃ እንዲያደርሱ እንዲያደርጉልን እንጠይቃለን፡፡
  3. በጉባኤው ለመሳተፍ ፈቃደኛ የሆኑትን ተሳታፊዎች ዝግጅት መከታተል ለጉዟቸው የሚያስፈልጋቸውን ትራንስፖርትና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማመቻቸት በጉባኤ ወቅት ተሳትፎአቸውን መከታተል የሚመለሱበትንም መከታተል ማረጋገጥ::

ማሳሰቢያ 3- ደብረ ቅዱሳን ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን

  1. ለተሳታፊዎች ምግብና መጠጥ ያዘጋጃል::
  2. በምእመናን ቤት ለማደር ፍቃደኛ ለሆኑት የማደሪያ ቦታ ያመቻቻል ።
  3. ተሳሳፊዎች በከተማ ውስጥ ለሚያደርጓቸው ጉብኝቶች የትራንስፖርት ሁኔታን ያመቻቻል አስጎብኝ ይመድባል ።

ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በሚቀጥለው የስልክ ቁጥር ወይም የኢሜል አድራሻ ጥያቄዎችን መላክ ወይም መጠየቅ ይችላል:

  • አካለወልድ ታደሰ- በሰበካ ጉባኤ የሰንበት ትምህርት ቤት ተጠሪ (ስ 613 712 5852 ኢ= akalewoldtejitu@gmail.com)
  • ብሩክ ውበቴ – የሰበካ ጉባኤ ፀሐፊ (ስ 613 315 8987 ኢ- bruckwendu@gmail.com )

Details

Start:
August 29
End:
August 31
Event Category:

Organizer

SaintTeklehaimanotChruch
Email
admin@stteklehaimanotottawa.org

Venue

Chruch
915 Merivale Road
Ottawa, Ontario K1Z 6A1 Canada
+ Google Map

Leave A Reply

This content is protected by St. Teklehaimanot Church. Please contact us for permission.