ነገረ ቅዱሳን
ቅዱስ ማለት
ቅድስና ራሱ በሁለት ይከፈላል
1. የባህሪ ቅድስና
ዘሌ. 19÷2 ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› እንዲል፡፡
መዝ. 137÷2 ‹‹ወደቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤ ስለምህረትህና ስለ እውነትህ ስምህን አመሰግናለሁ፤ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ከፍ ከፍ አድርገሀልና›› እንዲል፡፡
2. የጸጋ ቅድስና
መዝ. 32÷5 ‹‹ጽድቅና ፍርድን ይወድዳል የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች››
ሮሜ 8÷28 ‹‹እግዚአብሔር ለሚወድዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን›› እንዲል፡፡
ከላይ የተጠቀሱት የመጽሐፍ ቅዱስ ኃይለ ቃላት ውስጥ ቸርነት፣ በጐነት እያለ የተጠቀሰው የእግዚአብሔር የባህሪይ ገንዘቡ ስለሆነውና ከእግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለሚሰጠው የጸጋ ቅድስና ነው፡፡ ስለዚህ የቅድስና ጥሪ ለሰው ዘር ሁሉ የተላለፈ ጥሪ ቢሆንም የተቀበሉትና በሕይወት የኖሩበት ጥቂቶች ናቸው፡፡
ማቴ. 22÷14 ‹‹የተጠሩ ብዙዎች፣ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና›› እንዲል፡፡
ነገረ ቅዱሳን ማለት ምን ማለት ነው?
‹‹ነገረ ቅዱሳን›› ማለት፡- ቅዱሳን ከልደታቸው እስከ እረፍታቸው ድረስ በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ ሕገ እግዚአብሔርን አክብረው፣ ትእዛዙን ፈጽመው የኖሩና የሚኖሩ የእግዚአብሔር ልጆችን እንዲሁ የቅዱሳንን መላእክትን ነገር የምንማርበት ትምህርት ቤት ነው፡፡
አንድም ነገረ ቅዱሳን ስንል፡- ኃይማኖት ይዘው ምግባር ሠርተው በስርዓት ተጉዘው እስከሞት ድርስ ታምነው ለተገኙ የእግዚአብሔር ወጃጆች፣ ንጹሐን መላእክት ክብሩን እንደገለጸላቸውና እንደሚገልጽላቸው የሚያስረዳን ነው፡፡
ነገረ ቅዱሳንን መማር (ማወቅ) ለምን አስፈለገ?
ቅዱሳንን ማወቃችን ምን ጥቅም አለው?
ቤተክርስቲያን ቅዱሳን የምትላቸው እነማንን ነው?
ኢሣ. 6÷3 ‹‹አንዱም ለአንዱ፣ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያሉ ይጮሁ ነበር፡፡›› ስለዚህ በባህሪዩ ቅዱስ የሆነውን እግዚአብሔርን ስለሚያመሰግኑ፣ ስለሚቀዱሱ ቅዱሳን ተብለዋል፡፡
2ኛ ጴጥ 1÷25 ‹‹ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፣ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ›› እንዲል፡፡
ዮሐ. 17÷17-19 ‹‹በእውነት ቀድሳቸው ቃልህ እውነት ነው፡፡ ወደዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደዓለም ላክኋቸው፤ እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንደሆኑ እኔ ራሴን ስለእነርሱ እቀድሳለሁ››
ማቴ 10÷42 ‹‹ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ያገኛል›› እንዲል፡፡
ሮሜ 10÷15 ‹‹መልካሙን የምስራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው››
ኢያሱ 5÷15 ‹‹የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ኢያሱን፡- አንተ የቆምክባት ስፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን ከእግር አውልቅ አለው››
ቅዱሳን መጻሕፍት ቅዱስ መሰኘታቸው የሰውን ልጅ መነሻና መድረሻ ታሪክ በሦስቱም ሕግጋት የተነሱ ቅዱሳን ጥንተ ክብራቸውን ገድላቸውን ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን ጸጋ እግዚአብሔር ወልድ የሰውን ልጅ ለማዳን ያደረገውን ጉዞ የማዳን ሥራውን ስለያዙ ቅዱሳን ተባሉ፡፡
ሥጋዊውን ዓለም ከሚያንጸባርቁ ዓለማውያን ሥዕላት ፈጽመው የተለዩ በመሆናቸው ነው፡፡ የቅዲሳኑ ቅድስና ሥዕላቱንም ቅዱሳት አሰኝቷቸዋል ሥዕላቱ በራሳቸው የሚያደርጉት ገቢረ ተአምራት ቅዱሳት አሰኝቷቸዋል፡፡
(ቅዱስ ያሬድ ስለመስቀሉ በድጓ ዘክረምት ላይ እንዲህ ብሏል) ‹‹የቅዱሳን ክብራቸው የጻድቃን ሞገሳቸው የዕውራን ብርሃናቸው እነሆ ይህ መስቀል ነው›› ብሏል፡፡
ታቦት ማለት በግእዝ ቋንቋ ማዳሪያ፣ ማዳኛ ማለት ሲሆን በዚህ ታቦት ላይ እግዚአብሔር የሚያድርበትና የሚገለጥበት የጽላት ሕጉ ማዳሪያ ነው፡፡ ዘፀ. 25÷22
የቅዱሳን መታሰቢያ በቤተክርስቲያን
ዕብ. 6÷10 ‹‹እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ አመጸኛ አይደለምና፡፡›› ዕብ. 11÷32……
ኢሣ. 56÷5 ‹‹በቤቴና በቅጽሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋልሁ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ፡፡››
ማጠቃለያ እግዚአብሔር ከ22ቱ ስነፍጥረት በቅድስና ማዕረግ ስሙን ቀድሰው ክብሩን እንዲወርሱ አድርገው የፈጠራቸው ቅዱሳን መላእክትንና፣ የሰው ልጅን ነው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
2006 ዓ.ም © የመ/ገ/ጽ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ ሰንበት ትምሕርት ቤት